ኮሌጁ በጠንካራ የሥራ አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ

Posted 2021-02-05 07:46:53
News image

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቴክኒክና ሙያና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ከጥቅምት 11እስከ ጥቅምት 12/2013 በባህርዳር ከተማ ባዘጋጀው መድረክ የዘርፉን የ2013 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በማካሄድ የ2013 በጀት ዓመቱን የቀሪ 9 ወራት የዕቅድ ትውውቅ አድርጓል፡፡ በሥራ አፈጻጸም ግምገማና በእቅድ ትውውቅ መድረኩ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች አመራሮች፤ የዞን ቴክኒክና ሙያና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን ክልሉ በሥሩ የሚገኙ 120 ኮሌጆና ፖሊቴክኒክ ኮሌጆችን በማወዳደር የላቀ አፈጻጸም ላሳዩት የእውቅና ሰርትፍኬት ከመስጠት በተጨማሪ ዴስክቶፕ ኮምፒዩተር፤ ፕሪንተርና የላፕቶፕ ቁሳቁስ ሽልማቶችን ሰጥቷል፡፡ የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በነበረው የላቀ አፈጻጸም 3ኛ ደረጃ በመውጣቱ የሰርትፍኬትና የፕሪንተር ማሽን ተሸላሚ ሆኗል፡፡

ኮሌጁ በጠንካራ የሥራ አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ

News

News image
2022-08-17 17:21:05
በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂና የሪፎርም አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ የተዘጋጀ ስልጠና በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መሰጠት ጀመረ
News image
2022-08-02 12:52:41
የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞችና ሰልጣኞች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አካሄዱ
News image
2022-08-02 12:46:41
የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2014 እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የ90 ቀናት እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ
Kombolcha Polytechnic College