የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በድግሪና በተለያዩ የብቃት ደረጃዎች ያሰለጠናቸውን ከ850 በላይ ሰልጣኞችን አስመረቀ

Posted 2021-03-01 04:27:07
News image

የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በኮሮና ምክንያት ተቀቋርጦ የነበረውን ስልጠና በማካካስ ከብቃት ደረጃ I እስከ ደረጃ IV ባሉ የተለያዩ የሙያ መስኮችና በድግሪ መርሀ ግብር ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች የካቲት 20 ቀን 2013 አስመረቀ፡፡ ኮሌጁ ከደረጃ I እስከ ደረጃ IV ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች (ወ 426፤ ሴ፤ 295፤ ድ– 721) ለ14ኛ ጊዜ እንዲሁም በማኑፋክቸሪንግ፤ በአውቶሞቲቭና በኤሌክትሲቲ/ኤሌክትሮኒክስ ዘርፍ በድግሪ ፕሮግራም (ወ- ሴ– 14 ድ-136) ለ2ኛ ጊዜ በአጠቃላይ 857 ሰልጣኞች አስመርቋል፡፡ በምረቃ ስርዐቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ መላኩ አራጋው ኮሌጁ ከተመሰረተበት 1994 ጀምሮ ላለፉት 19 ዓመታት ከአስራ አራት ሺህ ስምንት መቶ በላይ ሰልጣኞችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ በቅጥርም ይሁን በመደራጀትና በግል ሥራ ፈጠራ ወደ ሥራ ተሰማርተዋል ብለዋል፡፡ ማስመረቅ የኮሌጁ የመጨረሻ ግብ አይደለም ያሉት የኮሌጁ ዲን ሁሉም ምሩቃን በሀገር ደረጃ አስከ 90 ፐርሰንት የሚሆኑት ተመራቂዎች በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የሥራ ባለቤት እንዲሆኑ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት እንሠራለን ብለዋል፡፡ ሀገራችን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ተርታ ለማሰለፍና ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመገንባት የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ሴክተር ላይ ከፍተኛ ኃላፊነት መጣሉን ገልጸው ይኽንም ኃላፊነት ለመወጣት ኮሌጁ ቆርጦ በመነሳት ኢኮኖሚው የሚፈጥራቸውን ኢንዱስትሪዎች ሊሸከም የሚችል በሙያ ክህሎቱና ብቃቱ የተረጋገጠ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት በኩል የፊናውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል፡፡

የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በድግሪና በተለያዩ የብቃት ደረጃዎች ያሰለጠናቸውን ከ850 በላይ ሰልጣኞችን አስመረቀ

News

News image
2022-08-17 17:21:05
በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂና የሪፎርም አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ የተዘጋጀ ስልጠና በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መሰጠት ጀመረ
News image
2022-08-02 12:52:41
የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞችና ሰልጣኞች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አካሄዱ
News image
2022-08-02 12:46:41
የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2014 እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የ90 ቀናት እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ
Kombolcha Polytechnic College