በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የፕሮጀክት ግንባታ ማሰጀመሪያ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

Posted 2021-06-12 00:53:38
News image

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር በአምስት ዓመታት ውስጥ ግንባታቸው ተጠናቆ ወደስራ የሚገቡ ሰባት የምስራቅ አፍሪካ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ማሰልጠኛ የልህቀት ማእከላትን ከ150 ሚሊየን ዶላር በላይ መድቦ በተለያዩ አካባቢዎች እያስገነባና እያጠናከረ ይገኛል፡፡ ከግንባታዎቹ መካከል አንዱ የሆነው የኮምቦልቻ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ልህቀት ማእከል የመሰረት ድንጋይ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ ሰኔ 02/2013 ዓ/ም የተቀመጠ ሲሆን ግንባታዉ በ12.85 ሚሊየን ዶላር ይካሄዳል፡፡ የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ የስልጠና ዘርፍ የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችለውን የፕሮጀክት ግንባታ የማሰጀመሪያ መርሀ ግብር ከፍተኛ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ መስተዳድር የመንግስት ባለስልጣኖች በተገኙበት አካሂዷል። የኮምቦልቻ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ መላኩ አራጋዉ የልህቀት ማእከላቱ መገንባት የትምህርት ግብአትን በሟሟላት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና በገበያ ተፈላጊ የሆነ የሰው ሃይል ለማሰልጠን ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል፡፡

በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የፕሮጀክት ግንባታ ማሰጀመሪያ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

News

News image
2022-08-17 17:21:05
በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂና የሪፎርም አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ የተዘጋጀ ስልጠና በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መሰጠት ጀመረ
News image
2022-08-02 12:52:41
የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞችና ሰልጣኞች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አካሄዱ
News image
2022-08-02 12:46:41
የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2014 እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የ90 ቀናት እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ
Kombolcha Polytechnic College