Kombolcha Polytechnic College
በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ያለንክኪ የሚሠራ የእጅ መታጠቢያ ቴክኖሎጂ ተተገበረ

Posted 2021-02-05 07:56:48

የኮሮና ቫይረስን እንዴት እከላከላለሁ? የኮሮና ቫይረስ መከላከያ እርምጃዎች:- አዘውትረን እጆቻችንን በውኃና በሳሙና ቢያንስ ለ20 ሴኮንዶች ያህል በሚገባበ ማሸትና ማፅዳት ፤ -ሲያስለንና ሲያስነጥሰን በሶፍት ወይም ክርናችንን በማጠፍ አፍና አፍንጫችንን መሸፈን ፤ አክታን በየቦተው አለመትፋት-ዐይንን አፍንጫንና አፍን ከመነካካት መቆጠብ ፤ ህዝብ በተሠበሠበበት አካባቢ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማሰከ (ጭንብል) መጠቀም-በኮሮና ቫይረስ ከተያዘም ሆነ ከታመመ ሰው ጋር በአካል የቀረበ ግንኙነት አለማድረግ ፤ አዘውትረን የምንጠቀምባቸውን የጋራ መገልገያ ቁሳቁሶች በአልኮል ወይም በሳኒታይዘር ማፅዳት የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች የተለመዱ...

Read More
የኮሌጁ ኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ የዓለም ባንክ ፕሮጀክት አፈጻጸም ያለበትን ሂደት ገመገመ

Posted 2021-02-05 07:50:05

የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን በአገር አቀፍና በምስራቅ አፍሪካ የልዕቀት ማዕከል ለማድረግ አመራሩ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን አዘጋጅቶ በማቅረብና ከሌሎች አቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ጋር ተወዳድሮ በማሸነፉ ኮሌጁን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከነዚህ ፕሮጀከቶች ውስጥ ኮሌጁን በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ ዘርፍ የልህቀት ማዕከል ለማድረግ ከዓለም ባንክ በተገኘ የ12.85 ሚሊዮን ዶላር በርካታ ተግባራትን ለማከናወን የተያዘው ፕሮጀክት ዋናው ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞ የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴና ተግባራዊነት የሚከታተል የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ ቀደም ሲል የተቋቋመ ሲሆን ቦርዱ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ያለበትን ሂደት...

Read More
ኮሌጁ በጠንካራ የሥራ አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ

Posted 2021-02-05 07:46:53

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቴክኒክና ሙያና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ከጥቅምት 11እስከ ጥቅምት 12/2013 በባህርዳር ከተማ ባዘጋጀው መድረክ የዘርፉን የ2013 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በማካሄድ የ2013 በጀት ዓመቱን የቀሪ 9 ወራት የዕቅድ ትውውቅ አድርጓል፡፡ በሥራ አፈጻጸም ግምገማና በእቅድ ትውውቅ መድረኩ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች አመራሮች፤ የዞን ቴክኒክና ሙያና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን ክልሉ በሥሩ የሚገኙ 120 ኮሌጆና ፖሊቴክኒክ ኮሌጆችን በማወዳደር የላቀ አፈጻጸም ላሳዩት የእውቅና ሰርትፍኬት ከመስጠት በተጨማሪ ዴስክቶፕ ኮምፒ...

Read More